እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው።

“….ይህ ሕዝብ በቀስታ የሚሄደውን የሰሌሆምን ውኃ ጠልቶአልና ሪአሶንንና የሮሜልዩንም ልጅ ወዶአልና ስለዚህ እነሆ ÷ እግዚአብሔር ብርቱና ብዙ የሆነውን የወንዝ ውኃ የአሦርን ንጉሥና ክብሩን ሁሉ ያመጣባቸዋል መስኖውንም ሁሉ ሞልቶ ይመጣል ÷ በዳሩም ሁሉ ላይ ይፈስሳል እየጎረፈም ወደ ይሁዳ ይገባል እያጥለቀለቀም ያልፋል ÷ እስከ አንገትም ይደርሳል አማኑኤል ሆይ ÷ የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች።
      አሕዛብ ሆይ ÷ እወቁና ደንግጡ እናንተም ምድራችሁ የራቀ ሁሉ ÷ አድምጡ ታጠቁ ደንግጡ ታጠቁ  ÷ ደንግጡ ። ተመካከሩ  ÷ ምክራችሁም ይፈታል ÷ ቃሉን ተናገሩ ÷ ቃሉም አይጸናም ። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነውና ። ” 
(ኢሳ  8 ÷ 6-10 ) ያንብቡ።
በዚህ ላይ ኢሳያስ በሚናገረው የእግዚአብሔርን የጥበቃውን  ኃይል ማየት የተሳነውን የይሁዳን ሕዝብ ያሳያል። የሚገርመው በጊዜው ይህ ሕዝብ ከጠባቂው አምላኩ ይልቅ በረአሶንና በሮሜልዩ ልጅ ደስታውን አድርጎ ነበር ።  እነዚህ ሰዎች ደግሞ ወገኖች ሳይሆኑ ጠላቶች ስለሆኑ  የይሁዳን ንጉስና ይሁዳን ሊወሩ የአሶር ንጉስ ሰራዊቶች ከኢየሩሳሌም በሰተቀር ሙሉ ይሁዳን እንደሚያጥለቀለቋት ነው ። የሚገርመው ግን አማኑኤል የተዋጠ ከሚመስለው ሕዝብ ጋር ነበር። ከዚያ በኋላ ነብዩ ምንም ቢበዙ እንኳን  እናንተ አሕዛብ ፎክሩ ይላቸዋል ። ፎክሩ ግን ደንግጡ። ለጦርነት ተዘጋጁ ግን ደንግጡ ፣ ለጦርነት ተዘጋጁ ግን ደንግጡ። ይላቸዋል። የሚፎክር እንዴት ነው የሚደነግጠዉ?  ለጦርነት የሚዘጋጅ ብርቱ ሰራዊት ያለው እንዴት ነው የሚደነግጥ?  ምድሪቱን እንደወራጅ ወንዝ ያጥለቀለቀ እንዴት ነው የሚደነግጥ?  የሚመካከሩ  ብቃት ያለቸውን የጦር መሪዎች ከመሳረያ ጋ ያለው እንዴት ነው የማይሳካለት?  በዕቅድና በፕላን የተነደፈ መዋቅር ያለውስ እንዴት ነው ንድፉ ፣የወጣው እቅዱ የማይጸናው ? ብዙ ጥያቄዎችን ልናነሳና ልናወጣ ልናወርድ እንችላለን። በዚህ ላይ ግን ለአሶር ንጉሥ ያልበራለት ሰራዊቱም ያልጠረጠረው ነገር ቢኖር ምንም እንኳን ይሁዳ ቢያጠፋ መጥፋቱ ግድ የሚለው ጠባቂ እና እረኛ የይሁዳ ጉዳይ የሚመለከተው ሁነኛ ንጉሥ ከንጉሥም ንጉሥ የነገሥታት ንጉሥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዳኛውና ጠበቃው ሕግ ሰጪውም የሆነ ከእርሱ ጋር እንደሆነ ነው። እረኛ እንደሌለው እንደተበተነ በግ ቢመስልም ይሁዳ በሚጠብቀው በአምላኩ ያልተጣለ ሕዝብ መሆኑን አልተገነዘበም ነበር።
    ሌላው የሚገርመው በጠላት ዘንድ ማስተዋል የሚባል ነገር የለም እንጅ የእስራኤል ጠባቂ እንደማይተኛና እንደማያንቀላፋ ዳዊት በዝማሬ ተቀኝቶት ነበር። የፍልስጤም ዋነኛ በትጥቅ የተሞላ ክንደ ብርቱ እንደተምዘግዛጊ የጦር መሳሪያ በራሱ ተምዘግዝጎ የሚውጥ የሚመስል ግዙፍ የባዕዳን ጀግና ትንሹን ብላቴና በንቀት ሲዝትበት በአንዲት ጠጠር ደፋ ብሎ እንዲቀር ያደረገውን የእግዚአብሔርን ገናናነት እና ዝና ማስታወስ አልቻሉም።
    ዛሬም ቢሆን ጠላቶቻችን ከእኛ ይልቅ ሰነፎች ናቸው። በጠላት ዛቻ የፈራህ ልብህም የደነገጠብህ ወገኔ ከሆነብህ ይልቅ ከአንተ ጋር ያለውን እግዚአብሔርን አስብ። ጠባቂህ እሚረታ እንጅ የሚረታ አይደለም። ኢየሱስ ክርስቶስን አንደ ሰው አትገምተው ሁሉን የሚረታ አምላክ ነውና።
      በይሁዳ ዘንድ ሁሉ የጠፋ ሲመስል እግዚአብሔር ግን ከእነሱ ጋር ነበረ። ጠላቶቻቸውንም አሽነፈ። ሃሌ ሉያ!  ዛሬም የአንተን / የአንችን ጠላት አማኑኤል በአብሮነቱ ያሽንፈዋልና በርቱ እንበርታ። እግዚአብሔር ይመስገን።  እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው  እና ድሉ የእኛ ነው ።  አሜን!!!

አትጨነቁ።

“….ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችልማን ነው ?……” (ማቲ 6 ÷ 26- 29 )
በመጨነቅ ጎዳና ላይ የምናጠበጥባቸው ብዙ በረከቶች አሉ። ለምሳሌ የሚጨነቅ ሰው
1 ሰላም የለውም።
2  እረፍቱን ያጣል።
3  ፍቅርን በቀላሉ ይጥላል።
4  አመፀኛም ይሆናል ማለት ሰውን የማይሰማ
     እልኸኛ የራሱን ሃሳብ ብቻ አሰተናጋጅ ይሆናል።
5   እግዚአብሐርን  መፍራት ይሰወርበትና      
የሚሰራው ሁሉ ትክክል ይመስለዋል።
6   ደስታውን የተቀማ ምስኪን ፍጡር ይሆናል።
7    በሰው መካከል ሆኖ ብቸኛ የሚሆን ፣ እንደሆነም አድርጎ የሚያስብ ይሆናል። ወዘተ
ታድያ እነዚህንና የመሳሰሉትን ጌታ ለሰው ልጆች ያዘጋጀውን የኑሮ በረከት በማጣት በጭንቀት ዓለም ውስጥ ዋታች እንዲሆኑ የአጅ አዙር እስረኛ ተጠቂ ዎች ይሆኑና ሰውም በቶሎ ስለማይረዳቸው አንድ አንዶቹ በሱስ ሌሎችን፣ በስርቆት ፣ ደግሞም በውሸት ይሞላቸውና ባላቸው ነገር ሳይረኩ ህይወትነም ሳያጣጥሙት ይቀራሉ።
ለዚህ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእኛ ጭንቀት የሚያመጣው ለውጥ እንዳሌለ አውቀን በጌታ በራሱ ለይ እነድናርፍ የሚያስተምረን። ልብ እንበል ሸክላ ከሰሪው  እንደማይበልጥ አኛም ለራሳችን ከሰራን አንበልጥምና የሚያስጨንቀንን በእርሱ ላይ እንጣለው። የሰላም አምላክም ከእኛ ጋር ይሆናል። ምርኰአችንንም ይመልስልናል። እርሱ የታመነና ፃድቅ በምህረት የተሞላ አምላክ ነውና።
” ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፣ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል። ”   ማቲ 6÷34
በቀረውስ በጌታ እና በሀይሉ ችሎት የበረታን እንሁን። የጌታ ፀጋና ፍፁም በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን  ።
            

አትጨነቁ

በብዙ ነገር እንጨነቃለን፣ በየእለቱም በሃሳብ እንዋትታለን። ሆኖም ብዙ ጭንቀታችን መሠረቱ የእኛ አቅምና ማንነት በእኛዉ እጅ ላይ አድርገን እንመለከትና ነገሩ እንዳሰብነው ሳይሆን ሲቀር በፍርሃት በመዋጥ ነው። ፍርሃት በራሱ ወደ አልፈለግነው አቅጣጫ የሚያጣድፍ መዘውር ነው። ታድያ ይህ አይነት ነገር በህይወታችን ሲከሰት ቆም ብሎ ልብን እና አእምሮ አረጋግቶ  ሁሉን ወደ  ሚያቀው ጌታ መለስ ብሎ ማሰብ አማራጭ የሌለው ይሆናል። መጽሐፍ ቅዱስ እ ንዲህ ብሎ አቅጣጫን ያሳየናል።

” ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ ፣ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ። ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ። ጌታ ቅርብ ነወ። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አት ጨነቁ።አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁ ንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።”
  (  ፊልጵ 4:4-7 )

መልካም ገና!!

ህጻን: ተወልዶልናል: ወንድ ልጅም: ተሰጥቶናልና: አለቅነትም: በጫንቃው: ላይ ይሆናል። ስሙም: ድንቅ መካር ፣ ሀያል: አምላክ ፣ የዘላለም አባት ፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል። ትንቢተ ኢሳ 9:6